Site icon www.zehabeshanews.com

ጌታቸው አሰፋን በተመለከተ

(ዘ-ሐበሻ ዜና) ጌታቸው አሰፋን በተመለከተ የተለያዩ መረጃዎች በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች የተለያዩ መረጃዎች እየተሰራጩ እንደሆነ ተመልክተናል። ብዙ የዘ-ሐበሻ ቤተሰቦችም መረጃውን እንድናጣራ ጠይቀውናል። ዘ-ሐበሻ ስለጌታቸው አሰፋ መገደል ከምንጮቹ እስካሁን ድረስ ለማረጋገጥ አልቻለም። በአማራ እና ትግራይ ክልል አቅጣጫ በሰቆጣ አቅጣጫ በርካታ የሕወሃት ሰዎች እንደተደመሰሱ መረጃው ዘ-ሀበሻ እጅ ያለ ሲሆን በጥቅሉ ጌታቸው ተገደለ የሚለውን ምንጮች ሊያረጋግጡልን አልቻሉም እንዳረጋገጡልን ለህዝብ ይፋ እናደርጋለን። ይጠብቁን፡:


ባለፈው ቅዳሜ ባሰራጨነው 3 መረጃዎች ላይ በዋግ አካባቢ ጌታቸው አሰፋ እና ጀነራል ታደሰ ወረደ በኮንቮይ ታጅበው መታየታቸው እና መከላከያው ሲመጣባቸው እንደሸሹ፤ ጌታቸው አሰፋም ቆስሎ እያነከሰ እንደሚሄድ ከተማረኩ የሕወሓት ወታደሮች መሰማቱን መዘገባችን ይታወሳል።

Exit mobile version