የኢትዮጵያ መንግስት አራት መቶ ሺህ ቶን ስንዴ ለመግዛት ዛሬ አለም አቀፍ ጨረታ አውጥቷል

የኢትዮጵያ መንግስት አራት መቶ ሺህ ቶን ስንዴ ለመግዛት ዛሬ አለም አቀፍ ጨረታ አውጥቷል፡፡ ይህ ጨረታ የሚዘጋበት ቀን ኦክቶበር 13 መሆኑን ኢሮፒያን ትሬደርስ አስታውቋል፡፡ ይህ የዛሬው ጨረታ በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ከአለም ገበያ በአጠቃላይ 680 ሺህ ቶን ስንዴ ለመግዛት መፈለጓን የሚያመላክት ነው፡፡

ስንዴ

ከዚህ ቀደም ሁለት መቶ ሺህ ስንዴ ለመግዛት ጨረታ ያወጣች ሲሆን ይህ ጨረታ የሚዘጋው ኦክቶበር 15 ነው፡፡ እንዲሁም ሰማኒያ ሺን ቶን ስንዴ ለመግዛት የወጣው ጨረታም የሚዘጋው ሴፕቴምበር 30 በመሆኑ ገና በእንጥልጥል ላይ ይገኛል፡፡ ባለፈው ሀምሌ ወር አራት መቶ ሺህ ቶን ስንዴ ለመግዛት የወጣው ጨረታ ችግር አለበት ተብሎ መሰረዙን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ ዛሬ የወጣው ጨረታም የተሰረዘው በድጋሚ ወጥቶ ነው፡፡